ክፍል 7 • የሐዋርያት ሥራ 18:23 እስከ 21:17
“በአደባባይና ከቤት ወደ ቤት . . . ማስተማር”
ሰዎችን ስናስተምር ትሑቶች መሆን እንዲሁም ሁኔታው የሚጠይቀውን ማስተካከያ ማድረግ የሚያስፈልገን ለምንድን ነው? ምሥራቹን የምንሰብክበት ዋነኛ መንገድ ምንድን ነው? ከግል ፍላጎታችን ይልቅ ለአምላክ ፈቃድ ትልቅ ቦታ እንደምንሰጥ ማሳየት የምንችለው እንዴት ነው? ጳውሎስ ስላደረገው ሦስተኛና የመጨረሻ ሚስዮናዊ ጉዞ የሚገልጸው አስደሳች ዘገባ ለእነዚህ ወሳኝ ጥያቄዎች መልስ ለማግኘት ያስችለናል።